አፍሪካ 90 በመቶ የሀብት እሴቷን ለምዕራባውያን ማቀነባበሪያዎች እንደምታጣ ኢትዮጵያዊው የምጣኔ ባለሙያ ገለጹ
18:32 07.06.2026 (የተሻሻለ: 18:34 07.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አፍሪካ 90 በመቶ የሀብት እሴቷን ለምዕራባውያን ማቀነባበሪያዎች እንደምታጣ ኢትዮጵያዊው የምጣኔ ባለሙያ ገለጹ
የአኅጉሪቱ ጥሬ ዕቃዎችን በቀጥታ ወደ ውጭ የመላክ ልምድ፤ ምዕራባውያን ሀገራት ከፍተኛውን እሴት እንዲወስዱ በማድረግ፤ ኢምንት ትርፍ እንደሚያስቀርላት በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ባለሙያ እና ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት መሐመድ ኢሳ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ባለሙያው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ብሪክስ እንደ መፍትሔ፦ ብሪክስን መቀላቀል የአፍሪካ ሀገራት ሀብቶቻቸውን በሀገር ውስጥ እንዲያቀናብሩ፣ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲያስቀምጡ እና በእሴት ጭማሪ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ሽግግር አማካኝነት 90 በመቶ የሚሆነውን ጥቅም መልሰው እንዲያገኙ ያስችላቸዋል።
የጋራ ተጠቃሚነት ትብብር፦ የብሪክስ አባላት በአነስተኛ ወጪ ቴክኖሎጂን ያጋራሉ። አፍሪካን ወደኋላ አስቀርተው ከነበሩት የምዕራባውያን ሞዴሎች በተለየ፤ ሩሲያ ዘላቂ ዲፕሎማሲን ለማዳበር ለቴክኖሎጂ ሽግግር እና ፈጠራ ምቹ ሁኔታን ትፈጥራለች።
ከዶላር ጥገኝነት የመላቀቅ ጥቅም፦ በሀገር ውስጥ ገንዘቦች መገበያየት የአሜሪካን ዶላር የበላይነት በመቀነስ፤ አፍሪካ ምርቶቿን በተሻለ ዋጋ እንድትሸጥ እና ባለብዙ ወገን የንግድ ግንኙነቶች እንዲጠናከሩ ያደርጋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X