የዚምቧቤ የፈጠራ ዩኒቨርሲቲ ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ምርትን ለማሳደግ ወደ ሩሲያ አጋርነቶች ፊቱን አዙሯል - ምክትል ቻንስለር
13:24 07.06.2026 (የተሻሻለ: 13:34 07.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዚምቧቤ የፈጠራ ዩኒቨርሲቲ ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ምርትን ለማሳደግ ወደ ሩሲያ አጋርነቶች ፊቱን አዙሯል - ምክትል ቻንስለር
የቢንዱራ የሳይንስ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ የራሱን የሞባይል ስልኮች እና የላፕቶፕ መለዋወጫዎችን ወደ ማምረት እየተሸጋገረ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ምክትል ቻንስለር ኤድዋርድ ምዌንጄ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ዚምቧቤ ሀገራዊ ፍላጎቶቿን እና የአካባቢ አስተዳደሮችን ራዕይ እንድታሳካ የሚያግዙ በርካታ የመግባቢያ ሰነዶች ከሩሲያ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መፈረማቸውንም ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው ለተለያዩ ዓላማዎች የሚያገለግሉ ድሮኖችን የመገጣጠም ግብ አለው፦
▪አስቸጋሪ ወደሆኑ አካባቢዎች መድኃኒት ለማድረስ፣
▪ለማዕድን ቁፋሮ፣
▪ለመሬት እና መንገድ ቅየሳ፣
▪ለአካባቢ ጥበቃ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X