ሩሲያን ለማግለል የተቀየሱ የምዕራባውያን እቅዶች ሙሉ በሙሉ ከሽፈዋል - የሉክሰምበርግ የአውሮፓ ፓርላማ አባል

ሰብስክራይብ
ሩሲያን ለማግለል የተቀየሱ የምዕራባውያን እቅዶች ሙሉ በሙሉ ከሽፈዋል - የሉክሰምበርግ የአውሮፓ ፓርላማ አባል

ፈርናንድ ካርትሃይሰር ከ #SPIEF 2026 ጎን ለጎን ለስፑትኒክ በሰጡት አስተያየት፤ "ይህንን እዚህ በሴንት ፒተርስበርግ ማየት ትችላላችሁ። ዛሬ መላው ዓለም እዚህ ይገኛል" ብለዋል።

ከመሣሪያ ሽያጭ ትርፍ የሚያጋብሱትን የወታደራዊ-ኢንዱስትሪ አካላት እንዲሁም አውሮፓን ከሩሲያ ጋር ወደ ግልጽ ግጭት ለመሳብ የሚፈልጉትን ጨምሮ፤ የጦርነት አዋጅ የሚጎስሙ ወገኖች የጦርነት ስጋትን እንደሚጨምሩ አስጠንቅቀዋል።

​አክለውም የኔቶ ተዓማኒነት እንደተነነና አሜሪካውያን ለአውሮፓ ጀርባቸውን በመስጠት ፊታቸውን ወደ ፓስፊክ ውቅያኖስ እያዞሩ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም ለአውሮፓ ከሩሲያ ጋር ከመነጋገር ውጭ ሌላ አማራጭ እንደማይተው ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0