በኢትዮጵያ ለባህላዊ ሕክምና የሚውሉ ዕፅዋት፣ መድኃኒት ለለመዱ ባክቴሪያዎች መፍትሔ መሆናቸውን አዲስ ጥናት አረጋገጠ

በኢትዮጵያ ለባህላዊ ሕክምና የሚውሉ ዕፅዋት፣ መድኃኒት ለለመዱ ባክቴሪያዎች መፍትሔ መሆናቸውን አዲስ ጥናት አረጋገጠ
በጌዴኦ ዞን የተካሄደው ይህ ጥናት፤ በልማድ ቁስልን ለማከም የሚዘወተሩት «አናሙሮ»፣ «ደማከሴ» እና «ጤና አዳም» በቤተ ሙከራ ሂደት፣ መድኃኒት የለመዱ ባክቴሪያዎችን የመከላከል ከፍተኛ አቅም እንዳላቸው መረጋገጡ አመላክቷል።
ጥናቱ በዲላ ዩኒቨርሲቲ፣ በተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ የምርምር ተቋማት ምሁራን ተጠንቶ በሳይንሳዊ ሪፖርቶች መጽሔት ላይ ዛሬ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ሆኗል፡፡
ዕፅዋቱ በተለይም ከተለያዩ የቁስል ዓይነቶች በተወሰዱና በአንቲባዮቲክስ መዳን ላልቻሉ አራት የባክቴሪያ ዝርያዎች ላይ ከፍተኛ የማጥፋትና የማዳከም ብቃት አሳይተዋል።
ዋና ዋና የምርምር ውጤቶች፦
▫ደማከሴ ፦ የደማከሴ ቅጠል የሜታኖል ውህድ እጅግ የላቀ ባክቴሪያን የማጥፋት አቅም በማሳየት በተለይም ለሕክምና አስቸጋሪ በሆኑት የቃጠሎ ቁስል ባክቴሪያ እና መድኃኒት በተላመዱ ዝርያዎች ላይ ፈጣን ውጤት አስመዝግቧል።
▫ ፈጣን የፈውስ ሂደት ፦ የደማከሴ ውህድ በተጠናከረ መጠን በ2 ሰዓታት ውስጥ ብቻ የባክቴሪያዎቹን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ የቻለ ሲሆን፥ በ4 እና 6 ሰዓታት ውስጥ ባክቴሪያዎቹን ሙሉ በሙሉ ማጥፋት ችሏል።
▫ የአናሙሮ እና ጤና አዳም ሚና፦ የአናሙሮ ስርና ግንዶች እንዲሁም የጤና አዳም ውህዶችም ባክቴሪያዎቹ እንዳይባዙ የማገድና የማጥፋት ተስፋ ሰጪ አቅም አሳይተዋል።
ጥናቱ በኢትዮጵያ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ የመጣውንና ለተለመዱ መድኃኒቶች የማይገዙ የቁስል ኢንፌክሽኖችን ለመከላከል አዳዲስ የሀገር በቀል መድኃኒቶችን ለማዘጋጀት እንደ ትልቅ መነሻ የሚያገለግል መሆኑ ተገልጿል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X