አፍሪካ ሀብቶች አሏት፣ ነገር ግን ‘የብዝበዛ መሬት’ እየሆነች ነው - የቶጎ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ
19:17 04.06.2026 (የተሻሻለ: 19:24 04.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አፍሪካ ሀብቶች አሏት፣ ነገር ግን ‘የብዝበዛ መሬት’ እየሆነች ነው - የቶጎ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ
“በቅኝ ገዥዎች ፍላጎት ጥገኝነት ስር እንዲቆይ የተደረገው ያልተሟላ የኢኮኖሚ ሥርዓት”፣ በኢኮኖሚው “መሠረታዊ የመንቀሳቀሻ ቁልፎች” አማካኝነት በአኅጉሪቱ ላይ ጫና ለመፍጠር እየሞከረ መሆኑን ሼ ሄሉ-ላውሰን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
የአፍሪካ አኅጉር የሚከተሉትን እምቅ ሀብቶች ይዟል፦
ወደ 30 በመቶ የሚጠጋውን የዓለም የማዕድን ክምችት፣
60 በመቶ ገደማ ያልታረሰ ሊታረስ የሚችል መሬት፣
ግዙፍ የኢነርጂ (የኃይል) ሀብቶች።
ነገር ግን፣ አኅጉሪቱ ከእነዚህ ሀብቶች ሙሉ በሙሉ ተጠቃሚ መሆን አለመቻሏን የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አፅንዖት ሰጥተው ገልጸዋል።
በምዕራባውያን አገራት የተፈጠረውን ይህንን አመለካከትና አካሄድ ለመለወጥ፣ ለአፍሪካ አገራት “አፍሪካን ለመለወጥ የሚያስችል ካፒታል እና የፖለቲካ ቁርጠኝነት” ያስፈልጋቸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X