ሩሲያ አፍሪካን ‘እንደ ዝቅተኛ ሳይሆን እንደ እኩል’ አጋር ታያለች - የማላዊ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ

ሰብስክራይብ

ሩሲያ አፍሪካን ‘እንደ ዝቅተኛ ሳይሆን እንደ እኩል’ አጋር ታያለች - የማላዊ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ

በማላዊ ብሔራዊ የዕቅድ ኮሚሽን የልማት ምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት ኦስቲን ቺንግዌንግዌ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፣ “ይህ እንደ አፍሪካ ልንጠቀምበት የሚገባ ዕድል ነው፤” የኢኮኖሚ አማራጮችን በማስፋፋት አዳዲስ ዕድሎችን ማግኘት እና “የአፍሪካን ኢኮኖሚ ወደ ላቀ ደረጃ ማዘጋጀት” ያስፈልጋል።

አሁን ያለው “የፋይናንስና የኢኮኖሚ ሥርዓት አፍሪካውያንን በሚጠቅም መልኩ የተቀረጸ አይደለም” ሲሉ ጠቁመዋል።

ንደ ምጣኔ ሀብት ባለሙያው ገለጻ፣ አፍሪካ በሚከተሉት መንገዶች ራሷን ማደራጀት ይኖርባታል፦

🟠 የእያንዳንዱን ቀጣና “የማወዳደሪያ ብልጫ” በመለየት፣

🟠 ትናንሽ ኢኮኖሚዎችን እንደገና በማደራጀት እና በቀጣናዊ መሪዎች አማካኝነት “እንደ አንድ የጋራ ስብስብ በአንድ ድምፅ መናገርን” ማረጋገጥ፣

🟠 በአፍሪካ አገራት መካከል “ለተመሳሳይ ገበያዎች” የሚደረግን ፉክክር ማስወገድ፣

🟠 አሁን ባሉ መድረኮች ላይ “የፖለቲካ ቁርጠኝነትን” መፍጠር።

“የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣናን እንኳ ብንመለከት፣ ያለ ፖለቲካ ቁርጠኝነት በአፍሪካ ውስጥ ያሉ ዋና ዋና ተዋናዮችን ብቻ የሚጠቅም ይመስለኛል” ብለዋል።

ስለ አፍሪካ የማወዳደሪያ ብልጫዎች፣ ስለ አገራት ብሔራዊ ገንዘቦች አጠቃቀም እና የሴንት ፒተርስበርግ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ፎረም (#SPIEF2026) አፍሪካ አቋሟን እንድታሰማ እንዴት እንደሚያግዛት የበለጠ ለማወቅ ቪዲዮውን ይመልከቱ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0