የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ከርዕሰ ብሔር ታዬ አጽቀሥላሴ ጋር ውይይት አደረገ
20:32 03.06.2026 (የተሻሻለ: 20:34 03.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ከርዕሰ ብሔር ታዬ አጽቀሥላሴ ጋር ውይይት አደረገ
ርዕሰ ብሔር ታዬ በሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የውጭ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ብፁዕ አቡነ አንቶኒዮስ የተመራው ልዑካን ቡድን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ብፁዕ አቡነ አንቶኒዮስ ከፕሬዝዳንቱ ጋር የተሳካ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸው፤ በሩሲያ እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት መካከል ያለው ግንኙነት በሁለቱ አብያተ ክርስቲያናትም ሆነ ለሀገራቱ ዘላቂ ወዳጅነት ትልቅ ማረጋገጫ መሆኑን ጠቁመዋል።
በውይይቱ የተሳተፉት የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እንዲሁም የደቡብ ኦሞ እና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ በበኩላቸው፣ ይህ መንፈሳዊና ባህላዊ ትስስር በሕዝብ ለሕዝብ ዲፕሎማሲ ላይ በቅንጅት ለመሥራት የጎላ ፋይዳ እንዳለው አስረድተዋል፡፡
በውይይቱ ወቅት በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ተርኪንና ሌሎች የልዑኩ አባላት ተገኝተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia