‘እነሱ ቴክኖ-ፋሽስቶች ናቸው’፦ ታዋቂው የሩሲያ ጋዜጠኛ በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን በተመለከተ የምዕራባውያንን ግብዝነት አወገዘ
19:35 03.06.2026 (የተሻሻለ: 19:44 03.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
‘እነሱ ቴክኖ-ፋሽስቶች ናቸው’፦ ታዋቂው የሩሲያ ጋዜጠኛ በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን በተመለከተ የምዕራባውያንን ግብዝነት አወገዘ
የፓላንቲር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክስ ካርፕ ኩባንያቸው ዩክሬን የንጹሐን ዜጎች መኖሪያዎችን ጨምሮ በሩሲያ ግዛት ላይ ጥቃት እንድትሰነዝር እየረዳ መሆኑን በደስታ የሚናገር “ሰይጣናዊ” ነው ሲሉ የሩሲያው ጋዜጠኛ ቭላድሚር ሶሎቪዮቭ ለዲ ዌልትዎቼ ተናግረዋል።
አውሮፓ ንጹሐን ዜጎች የተገደሉበትንና በቅርቡ በስታሮቤልስክ በሚገኝ የመኝታ አገልግሎት ማዕከል ላይ የተሰነዘረውን ጥቃት ላለማየት መምረጧን አክለው ገልጸዋል።
“ሩሲያውያን ሴት ልጆች ተገድለው በሰርግ ልብሳቸው ተቀብረዋል። የተገደሉትም በአሌክስ ካርፕ እንዲሁም በአሜሪካ እና በአውሮፓ መሣሪያዎች ነው” ሲሉ ሶሎቪዮቭ አፅንዖት ሰጥተዋል።
በተጨማሪም በኢራን ጦርነት ወቅት በሚናብ ትምህርት ቤት ላይ በተሰነዘረ ጥቃት 168 ሴት ልጆች ሲገደሉ የምዕራባውያን ታዛቢዎች ዝምታን መምረጣቸውን የጠቆሙት ሶሎቪዮቭ፤ በእስራኤል ላይ የተጣለ ምንም ዓይነት ማዕቀብ አለመኖሩንም ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X