- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር፦ ውኃ የአፍሮ-ዲያስፖራ የጋራ ቅርስ

ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር፦ ውኃ የአፍሮ-ዲያስፖራ የጋራ ቅርስ
ሰብስክራይብ
"ውኃ ለአፍሪካ እና ለአፍሮ-ዲያስፖራው ከቀላል የተፈጥሮ ሃብትነት ባለፈ፣ አህጉራትንና ትውልዶችን የሚያገናኝ ታሪካዊ፣ ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ድልድይ ነው። ሳይንስን ከባህል፣ ቴክኖሎጂን ከአካባቢያዊ እውቀት ጋር በማጣመር የአየር ንብረት መረጃ ሉዓላዊነታችንን ማረጋገጥ እና በግሎባል ሳውዝ አገራት መካከል ጠንካራ ትብብር መፍጠር ይኖርብናል፡፡" ሲሉ የኢትዮጵያ ኦሽን ኢንስቲትዩት ተባባሪ መስራች እና ዋና ስራ አስፈፃሚ ኪዳን ኒኪታ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ "የሰማያዊ ኢኮኖሚዎችን ማስተሳሰር፦ አፍሪካን እና አፍሮ-ዲያስፖራን በውኃ ማገናኘት" በሚል ዋና ርዕስ ዙሪያ የውቅያኖስ ሳይንቲስት እና የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ባዮሎጂስት ከሆኑት ከኪዳን ኒኪታ ጋር ሰፊ ውይይት ያደረግን ሲሆን፤ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአካባቢ ጥበቃ አስተዳደር እና ዘላቂ ልማት ዓለም አቀፍ ግንኙነቶችን በድጋሚ በባረቁበት በዚህ ወቅት፣ ያልተማከሉ የሳይንስ ግኝቶች፣ ተንቀሳቃሽ ላብራቶሪዎች "Lab in a Bag" እና የደቡብ-ደቡብ ትብብር ምን ያህል ለውጥ እያመጡ እንደሆነ እንቃኛለን። በሌላ በኩል ደግሞ፣ የሰማያዊ ፣ የአረንጓዴ እና የፈጠራ/የካሮት ኢኮኖሚዎች ትስስር ለአፍሪካ ወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ እና ለአካባቢ መላመድ ያለውን ወሳኝ ሚና በዝርዝር ዳሰናል።

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን መረጃ ያድምጡ ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0