የሩሲያ ጦር ተማሪዎች ላይ ለተፈጸመው የሽብር ጥቃት ምላሽ የሚሆን ከፍተኛ የአጸፋ ጥቃት በኪዬቭ ላይ ፈጸመ - መከላከያ ሚኒስቴር
17:30 02.06.2026 (የተሻሻለ: 17:34 02.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሩሲያ ጦር ተማሪዎች ላይ ለተፈጸመው የሽብር ጥቃት ምላሽ የሚሆን ከፍተኛ የአጸፋ ጥቃት በኪዬቭ ላይ ፈጸመ - መከላከያ ሚኒስቴር
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፤ ወታደራዊ ኃይሉ በኪዬቭ የሚገኙ 10 የመከላከያ ማምረቻ ተቋማትን መትቷል።
ከሚኒስቴሩ የተገኙ ዋና ዋና ነጥቦች፦
በኪዬቭ ኢላማ ከተደረጉት 10 ተቋማት መካከል የመከላከያ ኢንዱስትሪ ማኅበራት፣ የራዲዮ ኤሌክትሮኒክስ ኢንተርፕራይዞች እና የመንግሥት ወታደራዊ ወደ ውጭ መላኪያ ኩባንያዎች ይገኙበታል።
በተጨማሪም በኪዬቭ የሚገኙ ሦስት ወታደራዊ የቅጥርና ምልመላ ማዕከላት ተመተዋል።
በዛፖሮዢዬ፣ ዲኔፕሮፔትሮቭስክ፣ ካርኪቭ፣ ሱሚ፣ ኽሜልኒትስኪ እና ፖልታቫ ክልሎች የተፈጸሙ ጥቃቶች የአየር ላይ ተሽከርካሪ አካላትን፣ የሰው አልባ ድሮን እና የሚሳኤል ሥርዓቶችን የሚያመርቱ የመከላከያ ኢንዱስትሪ ተቋማትን፣ እንዲሁም የሎጅስቲክስ ማዕከላትን እና የኢነርጂ መሠረተ ልማቶችን መትተዋል።
ስለ ስታሮቤልስክ አሳዛኝ ጥቃት እና ተያያዥ ጉዳዮችን የበለጠ ለማወቅ የስፑትኒክ አፍሪካን ትንታኔ ያንብቡ!
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X