ማሊ እና ቡርኪና ፋሶ ‘የአሸባሪዎችን የመሰረግ ሙከራዎች ያከሽፋሉ’ - የማሊ ፓርላማ አባል

ሰብስክራይብ

ማሊ እና ቡርኪና ፋሶ ‘የአሸባሪዎችን የመሰረግ ሙከራዎች ያከሽፋሉ’ - የማሊ ፓርላማ አባል

የቡርኪና ፋሶ የደኅንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና በባማኮ ያደረጉት ጉብኝት፣ በድንበር ጥበቃ ዙሪያ ያለውን ትብብር ለማጠናከር ያለመ ነው ሲሉ የማሊ ብሔራዊ የሽግግር ምክር ቤት የመከላከያ እና ደኅንነት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር ፉሴይኑ ዋታራ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፦

“በአንዳንድ አካባቢዎች ድንበሮቻችን በብዛት ክፍት ናቸው። ባለፈው ሚያዝያ 17 ቀን በተፈጸሙት ጥቃቶች ወቅት፣ በርካታ አሸባሪዎች የደኅንነት ኃይሎችን ትኩረት ሳይስቡ ወደ ከተሞቻችን መግባት መቻላቸውን አይተናል። እነዚህ ትልቅ ትምህርት የተወሰደባቸው ክስተቶች ናቸው” ብለዋል።

ℹ መረጃዎችን በጋራ መለዋወጥ የአሸባሪዎችን ማንነት እና መገለጫዎችን በቀላሉ ለመለየት እንደሚያግዝም ምክትል ሊቀመንበሩ አክለው ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0