የሞዛምቢክ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም የኢትዮጵያ አየር ኃይልን የቴክኖሎጂ አቅምና የልማት ሥራዎች ጎበኙ
18:46 01.06.2026 (የተሻሻለ: 19:04 01.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሞዛምቢክ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም የኢትዮጵያ አየር ኃይልን የቴክኖሎጂ አቅምና የልማት ሥራዎች ጎበኙ
በሞዛምቢክ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ጁሊዮ ዶስ ሳንቶስ ጄን የተመራ ከፍተኛ ወታደራዊ ልዑክ በኢትዮጵያ አየር ኃይል የሁለትዮሽ የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አድርጓል።
ልዑኩ የአየር ኃይሉን የሥልጠና ተቋማትና የከባድ ጥገና ማዕከልን የጎበኘ ሲሆን፤ አየር ኃይሉ እያስመዘገበ ባለው ፈጣን የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የሰው ኃይል ግንባታና ዘመናዊ መሠረተ ልማት መደነቁን ገልጿል።
በጉብኝቱ ወቅት በሁለቱ ሀገራት አየር ኃይሎች መካከል ያለውን የጋራ ተጠቃሚነትና ወታደራዊ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ፍሬያማ ውይይት መደረጉን የኢትዮጵያ መከላካያ ሠራዊት አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

1/4
© telegram sputnik_ethiopia

2/4
© telegram sputnik_ethiopia

3/4
© telegram sputnik_ethiopia

4/4
© telegram sputnik_ethiopia
1/4
© telegram sputnik_ethiopia
2/4
© telegram sputnik_ethiopia
3/4
© telegram sputnik_ethiopia
4/4
© telegram sputnik_ethiopia