በናይሮቢ የተቃውሞ ሰልፈኞች በሴቶች ላይ በሚፈጸም ግድያ እና በሕፃናት ጠለፋ ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠየቁ፦ ዘጋቢ

ሰብስክራይብ

በናይሮቢ የተቃውሞ ሰልፈኞች በሴቶች ላይ በሚፈጸም ግድያ እና በሕፃናት ጠለፋ ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠየቁ፦ ዘጋቢ

ሰኞ ዕለት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች “ሴቶችን እና ሕፃናትን መግደል ይቁም” በሚል መሪ ቃል ባደረጉት ሰልፍ የናይሮቢን መካከለኛ የንግድ ቀጣና እንቅስቃሴ ማስተጓጎላቸውን የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ ገልጿል። ሰልፉ የተካሄደው በኬንያ በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ግድያዎች እና የሕፃናት መጥፋት ድርጊቶች በከፍተኛ ሁኔታ መጨመራቸውን ለመቃወም ነው።

ነጭ፣ ሮዝ እና ሰማያዊ ልብሶችን የለበሱት ሰላማዊ ሰልፈኞቹ በቅርቡ የደረሱ ሰለባዎችን ለማሰብ አበባዎችን፣ ሻማዎችን እና ምሳሌያዊ የሬሳ ሣጥን በመያዝ በኬንያታ እና በሞይ አቬኑ ጎዳናዎች ላይ ተጉዘዋል።

አክቲቪስቶች መንግሥት በሴቶች ላይ የሚፈጸመውን ግድያ እንደ ሀገራዊ አስቸኳይ ጊዜ እንዲያውጅ እና እስካሁን እልባት ሳያገኙ የተከማቹ በሺዎች የሚቆጠሩ የሕፃናት ጠለፋ ጉዳዮችን ትኩረት ሰጥቶ እንዲፈታ እየወተወቱ ይገኛሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0