ፈረንሳይ ‘ታጎር’ የተሰኘችውን የነዳጅ ጫኝ መርከብ መያዟ እንደ ባሕር ላይ ወንብድና የሚቆጠር ነው - ክሬምሊን

ሰብስክራይብ

ፈረንሳይ ‘ታጎር’ የተሰኘችውን የነዳጅ ጫኝ መርከብ መያዟ እንደ ባሕር ላይ ወንብድና የሚቆጠር ነው - ክሬምሊን

የሩሲያ ፕሬዚዳንታዊ ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፤ “እነዚህን ዕርምጃዎች ሕገ-ወጥ እንደሆኑ አድርገን እንቆጥራቸዋለን፤ ድርጊቶቹ ከዓለም አቀፍ የባሕር ላይ ወንብድና ጋር የሚቀራረቡ ናቸው። ዕርምጃዎቹ ሙሉ በሙሉ ዓለም አቀፍ ሕግን በተከተለ መልኩ የተከናወኑ ናቸው ከሚለው መግለጫ ጋር ጨርሶ አንስማማም” ብለዋል።

ቃል አቀባዩ አክለውም፤ ሩሲያ ለተከሰተው ክስተት ምላሽ ለመስጠት የባሕር ላይ የጭነት ትራንስፖርት ደኅንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዕርምጃዎችን እንደምትወስድ ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም ኢማኑኤል ማክሮን በኤክስ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መረጃ፤ ፈረንሳይ ከእንግሊዝ እና ከሌሎች አጋሮቿ ጋር በመተባበር እሑድ ዕለት የነዳጅ ጫኝ መርከቧን መቆጣጠሯን አስታውቀው ነበር።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0