ማዳጋስካር ከሩሲያ ጋር ያላትን የወታደራዊ ግንኙነት ለደኅንነቷ እና ለሰላሟ ቀዳሚ ምርጫ መሆኑን አስታወቀች
14:55 01.06.2026 (የተሻሻለ: 15:04 01.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ማዳጋስካር ከሩሲያ ጋር ያላትን የወታደራዊ ግንኙነት ለደኅንነቷ እና ለሰላሟ ቀዳሚ ምርጫ መሆኑን አስታወቀች
የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሚካኤል ራንድሪያኒሪና፤ በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው የማዳጋስካር ወታደራዊ ትጥቅ እና መሣሪያዎች የሩሲያ ምርቶች መሆናቸውን ገልፀዋል።
▫ ሩሲያ እና ማዳጋስካር በቅርቡ ወታደራዊ ትብብራቸውን በማጠናከር የሩሲያ የአፍሪካ ኮርፕስ አሰልጣኞች ለ127 ለተመረጡ የማዳጋስካር ልዩ ኃይል አባላት ለ8 ሳምንታት የዘለቀ ሥልጠና የሰጡ ሲሆን፣ መሠረታዊ የድሮን አጠቃቀም እና የተኩስ ልምምድ ሥልጠናዎችንም አካትተዋል።
በተጨማሪም ሩሲያ ሁለት የ‘ቢኤምፒ-3’ ዘመናዊ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን (የጦር መኪኖችን)፣ የጦር መሣሪያ ጥይቶችን እና አነስተኛ የጦር መሣሪያዎችን ለሀገሪቱ በዕርዳታ አበርክታለች።
ቪዲዮው የየብስ ላይ የውጊያ ተሽከርካሪን፣ የታንክ አጥፊነትን እና በውኃ ላይ የመንሳፈፍ ብቃትን በአንድ ላይ ያቀፈውን ሁለገብ ‘ቢኤምፒ-3’ የታጠቀ የጦር መኪና የሙከራ እሽቅድድም ያሳያል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X