ኬንያውያን በአሜሪካ የቀረበውን የኢቦላ ለይቶ መቆያ ማዕከል ግንባታ በመቃወም አደባባይ ወጡ
14:25 01.06.2026 (የተሻሻለ: 14:34 01.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኬንያውያን በአሜሪካ የቀረበውን የኢቦላ ለይቶ መቆያ ማዕከል ግንባታ በመቃወም አደባባይ ወጡ
የኬንያ ጤና ሚኒስቴር በላይኪፒያ ካውንቲ ለአሜሪካ ዜጎች የሚሆን የኢቦላ ለይቶ ማቆያ ማዕከል ለመገንባት የያዘው ዕቅድ የሕዝብ ቁጣን ቀስቅሷል፤ በዚህም ሳቢያ በመቶዎች የሚቆጠሩ የናንዩኪ ነዋሪዎች ወደ አደባባይ በመውጣት ተቃውሟቸውን ማሰማታቸውን የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ ገልጿል።
የደኅንነት ስጋት ያለባቸው ተቃዋሚዎቹ በከፍተኛ ሁኔታ የሚንቀሳቀስበትን የናንዩኪ-ኔሪ አውራ ጎዳና ክፍሎችን በመዝጋት፤ መንግሥት ፕሮጀክቱን እንዲያቆም ጠይቀዋል። ይህም የሆነው ማዕከሉ የአካባቢውን ማኅበረሰብ ለአደገኛው የኢቦላ ቫይረስ ሊያጋልጥ ይችላል ከሚል ከፍተኛ ስጋት በመነጨ ነው።
ምንም እንኳን የኬንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የፕሮጀክቱን እንቅስቃሴ ለጊዜው ቢያግደውም፣ የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር ግን በፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ ሕጋዊ ይግባኝ ለማለት ማቀዱ ተገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X