የደቡብ አፍሪካ ራንድ በግንቦት ወር ከዶላር አንጻር ጠንካራ ከሆኑ ቀዳሚ መገበያያዎች ተርታ ተሰለፈ

ሰብስክራይብ

የደቡብ አፍሪካ ራንድ በግንቦት ወር ከዶላር አንጻር ጠንካራ ከሆኑ ቀዳሚ መገበያያዎች ተርታ ተሰለፈ

የደቡብ አፍሪካ ራንድ በግንቦት ወር ከአሜሪካ ዶላር አንጻር የ3.7 በመቶ ዕድገት በማሳየት በዓለም በሦስተኛ ደረጃ ከፍተኛ ጥንካሬ ያስመዘገበ መገበያያ እንዳደረገው ስፑትኒክ ከምንዛሬ መረጃዎች ያገኘው ትንተና አመልክቷል።

ማዕከላዊ ባንኩ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ቁልፍ የወለድ ምጣኔን ከፍ ማድረጉን ተከትሎ የሀገሪቱ ብሔራዊ ገንዘብ ሊጠነክር እንደቻለ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

በግንቦት ወር ከአሜሪካ ዶላር አንጻር ከፍተኛ ጥንካሬ ካሳዩት ሌሎች ቀዳሚ የገንዘብ ምንዛሬዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦

ሸቄል (የእስራኤል) — +6.1በመቶ፤

ሩብል (የሩሲያ) — +4.9 በመቶ፤

ፎሪንት (የሃንጋሪ) — +2.8 በመቶ፤

የኒውዚላንድ ዶላር — +2.0 በመቶ።

የደቡብ አፍሪካ ተቀማጭ ባንክ ገዢ ሌሴትጃ ካንያጎ በሚያዝያ ወር የዋጋ ግሽበት መጠን ከፍ ያለበትን ምክንያት ሲያብራሩ የሚያሳይ ቪዲዮ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0