በታንዛኒያ ባለፈው ዓመት ከአንድ ሺህ ቶን በላይ ዕፅ መያዙን ሚኒስትሩ ገለፁ
15:32 30.05.2026 (የተሻሻለ: 15:34 30.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በታንዛኒያ ባለፈው ዓመት ከአንድ ሺህ ቶን በላይ ዕፅ መያዙን ሚኒስትሩ ገለፁ
የታንዛኒያ ባለሥልጣናት በ2025 በአጠቃላይ 1074.72 ቶን አደንዛዥ ዕፅ መውረሳቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ደኤታ ፓላማጋምባ ካቡዲ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
የካናቢስ መያዝ መጠን ከ2024 ጋር ሲነጻጸር በ9.7 በመቶ (በግማሽ ገደማ) ቀንሷል። ይህ የሆነው የዕፅ እርሻዎችን የማውደም እና ሕዝባዊ የንቃተ ህሊና ማሳደጊያ ዘመቻዎች በመጠናከራቸው እንደሆነ ካቡዲ ገልጸዋል።
መንግሥት ከዕፅ ጋር የተያያዙ 1,124 መዝገቦችን ከፍቶ ክስ የመሠረተ ሲሆን በ1,058ቱ ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ አግኝቷል። እንዲሁም ከ1.25 ሚሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸው ንብረቶችን መውረሱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ከ85,000 በላይ ግለሰቦች የዕፅ ሱስ ሕክምና ዕርዳታ ያገኙ ሲሆን ሕዝባዊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶች ደግሞ ወደ 25 ሚሊዮን ለሚጠጉ ሰዎች መድረሳቸውንም አክለው ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X