የኢትዮጵያ ምርጫ ለሀገሪቱ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ አኅጉር ትልቅ ትርጉም አለው - የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ

ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ ምርጫ ለሀገሪቱ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ አኅጉር ትልቅ ትርጉም አለው - የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ

ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደውን 7ኛው ዙር ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ለመታዘብ አዲስ አበባ የገቡት የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪና የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፤ ምርጫው ከአፍሪካ ኅብረት ዋና መሥሪያ ቤት መገኛዋ የተሻገረ ወሳኝነት እንዳለው ገልጸዋል።

የኅብረቱ ታዛቢዎች ድምፅ አሰጣጡን ለመታዘብ ሙሉ ዝግጁ መሆናቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው የሕዝብ ነፃ ፈቃድ የሚንጸባረቅበት፣ ሰላማዊ፣ የሀገሪቱን የልማት ጉዞ የሚደግፍና ዴሞክራሲን የሚያሠርጽ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

ከ37 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና 73 ልዑካን ያሉት የታዛቢዎች ቡድንን የሚመሩት ኡሁሩ ኬንያታ፤ ከምርጫው ታዛቢነት ጎን ለጎን ከተለያዩ የምርጫ ባለድርሻ አካላትና ዲፕሎማቶች ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0