ኤኮዋስ የሳኅል ሀገራት ጥምረት ስኬቶች ግምት ውስጥ ማስገባት መጀመሩን የኒጀር ባለሥልጣን ገለፁ

ሰብስክራይብ

ኤኮዋስ የሳኅል ሀገራት ጥምረት ስኬቶች ግምት ውስጥ ማስገባት መጀመሩን የኒጀር ባለሥልጣን ገለፁ

በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ሊኖር የሚችለው ትብብር “ለኤኮዋስ የሳኅል ሀገራትን የሉዓላዊነት ጉዞ ለመገዳደር እንደ ሰበብ” ሊያገለግል አይገባም ሲሉ የኤም62 ንቅናቄ ብሔራዊ አስተባባሪ ሳኑሲ ማሃማን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

“ይህ ትብብር የውጭ ኃይሎች በአፍሪካ ሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ አለመግባት የሚለውን መርህ ባከበረ መልኩ እንዲከናወን እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው። ትብብሩ በሉዓላዊነት መርህ ላይ የተመሠረተ ሊሆን ይገባል።”

“የውስጥ አለመግባባቶች” ኤኮዋስን ማዳከማቸውን እንደቀጠሉ እና ሌሎች ሀገራትም የሳኅል ሀገራት ጥምረት ፈለግን ሊከተሉ ይችላሉ ሲሉም አክለዋል።

ℹ የኤኮዋስ አስታራቂ ላንሳና ኩያቴ ሰኞ ዕለት በቡርኪና ፋሶው ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ ዘንድ ቀርበው ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0