ከሺህ ዓመታት በፊት የጀመርነውን የጠፈር ምርምር እንድናቆም ማንም ሊመክረን አይችልም - ኢትዮጵያዊ የጠፈር ሳይንስ ተመራማሪ

© telegram sputnik_ethiopiaከሺህ ዓመታት በፊት የጀመርነውን የጠፈር ምርምር እንድናቆም ማንም ሊመክረን አይችልም - ኢትዮጵያዊ የጠፈር ሳይንስ ተመራማሪ
ከሺህ ዓመታት በፊት የጀመርነውን የጠፈር ምርምር እንድናቆም ማንም ሊመክረን አይችልም - ኢትዮጵያዊ የጠፈር ሳይንስ ተመራማሪ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.05.2026
ሰብስክራይብ
ከሺህ ዓመታት በፊት የጀመርነውን የጠፈር ምርምር እንድናቆም ማንም ሊመክረን አይችልም - ኢትዮጵያዊ የጠፈር ሳይንስ ተመራማሪ

በጠፈር ቴክኖሎጂ እና ሳይንስ ዘርፍ የሚደረጉ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብሮች ለኢትዮጵያም ሆነ ለመላው አፍሪካ የወደፊት ዕድገት ወሳኝ መሆናቸውን የአስትሮኖሚ ተመራማሪው ዶክተር ጌትነት ፈለቀ የብሪክስ የቴሌስኮፕ መረብን በተመለከተ ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል።


"ይህ የብሪክስ ቴሌስኮፕ መረብ በተለይም በሳይንስ፣ በምርምር፣ በህዋ ምርምር እና በሥነ ፈለክ ጥናት አማራጭ አካሄዶችን ይፈጥርልናል።"


በሌላ በኩል፤ "ሁልጊዜ በምዕራባውያን እርዳታ ላይ ጥገኛ መሆን ትልቅ ኪሳራ ነው" ያሉት ባለሙያው፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት ድጋፎች በመቋረጣቸው በዘርፉ የምርምር ሥራዎች ላይ መስተጓጎል እንደፈጠሩ አንስተዋል።


"እንደ ብሪክስ አስትሮኖሚ ዓይነት የትብብር ኔትወርክ ከፈጠርን ብዙ ነገሮችን ማድረግ እንችላለን። ሀገራችን፣ አፍሪካ እንዲሁም ሁሉም የብሪክስ ሀገራት ከዚህ ትብብር ብዙ ተጠቃሚ ሊሆኑ ይችላሉ።"


ታዳጊ ሀገራት ከሥነ-ፈለክ ምርምር ይልቅ በኢኮኖሚ ችግሮቻቸው ላይ ብቻ ማተኮር አለባቸው የሚሉ የምዕራባውያን ትችቶችንም በጽኑ ተቃውመዋል።


"እኛ የኮስሞስ ምርምርን የጀመርነው በዚህ ክፍለ ዘመን አይደለም፤ ከሺህ ዓመታት በፊት ነው። በመሆኑም ከሺህ ዓመታት በፊት የጀመርነውን ነገር እንድናቆም አሁን ማንም ሊመክረን አይችልም።"


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0