ኢትዮጵያ በድንበር ተሻጋሪ ውኃዎች ልማት ዙሪያ የጋራ ተጠቃሚነትን ለሚያረጋግጥ ትብብር ቁርጠኛ እንደሆነች በድጋሚ አረጋገጠች
16:32 29.05.2026 (የተሻሻለ: 19:14 29.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በድንበር ተሻጋሪ ውኃዎች ልማት ዙሪያ የጋራ ተጠቃሚነትን ለሚያረጋግጥ ትብብር ቁርጠኛ እንደሆነች በድጋሚ አረጋገጠች
63ኛውን የአፍሪካ ቀን በማስመልከት በአፍሪካ ኅብረት የ2026 ዓመታዊ መሪ ሃሳብ "የአጀንዳ 2063 ግቦችን ለማሳካት ዘላቂ የውሃ ተደራሽነትን እና አስተማማኝ የንፅህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ" ላይ ያተኮረ ጉባኤ በትናንትናው ዕለት ተካሂዷል።
በመድረኩ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ የሀገሪቱን የውሃ ደህንነትና አረንጓዴ ኢነርጂ ፍላጎት ከመመለስ ባለፈ፤ ለጎረቤት ሀገራት የሚተርፍ የኃይል አቅርቦትና ቀጣናዊ ትስስርን በመፍጠር ረገድ እየተጫወተ ያለው ሚና በምሳሌነት ቀርቧል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር አማካሪ ሞቱማ መቃሳ፤ በአኅጉሪቱ የሚገኙ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን ለማስተዳደር ቀጣናዊ ትብብር መጎልበት እንዳለበት ተናግረዋል።
“የጋራ የውሃ ሀብቶችን ለጠንካራ የሃይድሮ-ዲፕሎማሲ ሥራ መጠቀም ይገባል” ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

1/3
© telegram sputnik_ethiopia

2/3
© telegram sputnik_ethiopia

3/3
© telegram sputnik_ethiopia
1/3
© telegram sputnik_ethiopia
2/3
© telegram sputnik_ethiopia
3/3
© telegram sputnik_ethiopia