ውህደት ለዩሬዥያ ኢኮኖሚ ኀብረት አባል ሀገራት ተጨባጭ ጥቅሞችን እያስገኘ ነው - ፑቲን
16:04 29.05.2026 (የተሻሻለ: 16:14 29.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ውህደት ለዩሬዥያ ኢኮኖሚ ኀብረት አባል ሀገራት ተጨባጭ ጥቅሞችን እያስገኘ ነው - ፑቲን
የሩሲያ ፕሬዚዳንት በአስታና በተካሄደው የዩሬዥያ ጠቅላይ የኢኮኖሚ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ "ኅብረቱ ዕድገቱን ቀጥሏል" ብለዋል።
በፑቲን የተዘረዘሩ የቡድኑ ዋና ዋና ስኬቶች የሚከተሉት ናቸው፦
◻ በኅብረቱ ውስጥ ለሸቀጦች፣ ለአገልግሎቶች፣ ለካፒታል እና ለሰው ኃይል የሚሆኑ የጋራ ገበያዎች በከፍተኛ ደረጃ ተመስርተዋል፣
◻ የአባል ሀገራቱ ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ አመልካቾች አወንታዊ እንቅስቃሴ እያሳዩ ነው፣
◻ በአባል ሀገራቱ መካከል የሚደረጉ የንግድ ክፍያዎች በሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በሀገር ውስጥ ገንዘቦች እየተከናወኑ ነው፣
◻ አባል ሀገራቱ በአስፈላጊ የምግብ ምርቶች ራሳቸውን ለመቻል አቅደው እየሠሩ ነው፣
◻ የቡድኑ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ፍላጎትን በመሳቡ በርካታ ሀገራት እና ድርጅቶች ከኀብረቱ ጋር ለመተባበር ፍላጎታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፣
◻ የአባል ሀገራቱ የንግድ ልውውጥ እ.ኤ.አ በ2025 95 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፣
◻ ከሌሎች አባል ሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ለሩሲያ ፍጹም ቀዳሚ ተግባር ሆኖ ይቀጥላል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X