ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከዘጠኝ የብራዚል ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራረመ
13:48 29.05.2026 (የተሻሻለ: 14:24 29.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከዘጠኝ የብራዚል ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራረመ
ፊርማው በመጀመሪያው የብራዚል-አፍሪካ የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ጉባኤ ላይ እንደተፈረመ ታውቋል፡፡
ስምምነቱ የሚከተሉትን ስትራቴጂካዊ ዘርፎች አካቷል፦
◾ግብርና፣
◾ሕክምና፣
◾ሰብዓዊ ሳይንስ፣
◾ቴክኖሎጂና ሰው ሠራሽ አስተውህሎት፣
◾ኢነርጂ።
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ሥልጠና፣ ምርምር እና የማኅበረሰብ አገልግሎትን በማቀናጀት ፈር ቀዳጅ የሆነውን “ማኅበረሰብ-ተኮር ትምህርት” ፍልስፍና በጉባዔው ላይ እንዳቀረበ እና የብራዚል ዩኒቨርሲቲዎች ሞዴሉን ለመተግበር ጠንካራ ፍላጎት እንዳሳዩ አስታውቋል።
በብራዚል የትምህርት ሚኒስቴር በተዘጋጀው በዚህ ጉባኤ፤ ከ70 የብራዚል ዩኒቨርሲቲ ኃላፊዎችና እና ከ64 የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ተወካዮች ተሳትፈዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia