ካሜሩን እስከ 2035 ቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ የማዋል ምጣኔዋን ከ30 በመቶ በላይ ለማሳደግ እና የጥሬ ዕቃ ግዢን ለመቀነስ አቅዳለች - ባለሥልጣን

© telegram sputnik_ethiopiaካሜሩን እስከ 2035 ቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ የማዋል ምጣኔዋን ከ30 በመቶ በላይ ለማሳደግ እና የጥሬ ዕቃ ግዢን ለመቀነስ አቅዳለች - ባለሥልጣን
ካሜሩን እስከ 2035 ቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ የማዋል ምጣኔዋን ከ30 በመቶ በላይ ለማሳደግ እና የጥሬ ዕቃ ግዢን ለመቀነስ አቅዳለች - ባለሥልጣን - Sputnik አፍሪካ, 1920, 28.05.2026
ሰብስክራይብ

ካሜሩን እስከ 2035 ቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ የማዋል ምጣኔዋን ከ30 በመቶ በላይ ለማሳደግ እና የጥሬ ዕቃ ግዢን ለመቀነስ አቅዳለች - ባለሥልጣን

​ ካሜሩን "ጥሬ ዕቃውም ሆነ ገበያው" ስላላት ቆሻሻን ወደ ንግድ ሀብት መለወጥ ትችላለች ሲሉ የካሜሩን የተፈጥሮ፣ የአካባቢ ጥበቃ እና ዘላቂ ልማት ጥምረት ፕሬዝዳንት ፍራንክ ሩሰል አቴባ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

እንደ ኃላፊው ገለጻ፤ ብሔራዊ ዕቅዱ በትኩረት የሚሠራባቸው አራት ዘርፎች የሚከተሉት ናቸው፡-

​🟠 የግብርና-ኢንዱስትሪ፣

🟠 የፕላስቲክ ቆሻሻ፣

🟠 የደን ልማት፣

🟠 የዕንጨት ሥራ።

አገልግሎት የሰጠ ፕላስቲክን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል የድንጋይ ንጣፎችን እና ቧንቧዎችን የማምረት ሥራዎች ከወዲሁ እየተከናወኑ እንደሚገኙ አቴባ ጠቁመዋል።

​“ተፈጥሯዊ ቆሻሻ ከጠቅላላው ቆሻሻችን 60 በመቶ የሚሆነውን ይሸፍናል፤ ይህንን ደግሞ ወደ ማዳበሪያና ባዮጋዝ መቀየር ይቻላል።”

​ የካሜሩን ቆሻሻን መልሶ ጥቅም ላይ ማዋል ምጣኔ አሁን ላይ ከ10 በመቶ በታች መሆኑን የገለጹት አቴባ፤ የቆሻሻ ማቀነባበር ሥራን ለማስፋፋት የሚደረጉ ጥረቶች እ.ኤ.አ እስከ 2035 ድረስ 300 በመልሶ ማልማት-ኢኮኖሚ ላይ የሚሠ ሩ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ለመፍጠርና ለማደራጀት ከተያዘው ዕቅድ ጋር የተያያዙ መሆናቸውን አክለው ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0