ዘለንስኪ በምንም መልኩ ሂትለር ላይ ባይደርስም በሦስተኛ ተርታ ፊልም ገፀ-ባህሪውን መጫወት ይችላል - የሩሲያ የውጭ መረጃ አገልግሎት ኃላፊ

ዘለንስኪ በምንም መልኩ ሂትለር ላይ ባይደርስም በሦስተኛ ተርታ ፊልም ገፀ-ባህሪውን መጫወት ይችላል - የሩሲያ የውጭ መረጃ አገልግሎት ኃላፊ
ሰርጌ ናሪሽኪን በዓለም አቀፉ የደህንነት ፎረም ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
▪ በርካታ የዘመናችን ፖለቲከኞች ገንቢ ድርድሮችን የማካሄድ ብቃታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መምጣቱን እያሳዩ ነው፣
▪ አውሮፓ የዓለም አቀፍ ግጭት ማዕከል ለመሆን በከፍተኛ ፍጥነት እየገሰገሰች ነው፣
▪ የአውሮፓ ኅብረት በከፍተኛ ሁኔታ እየታጠቀ ባለበት ወቅት የጦርነት "ጉሰማ" በተለይ በአውሮፓ አይሎ እየተደመጠ ነው፣
▪ የአውሮፓ ልሂቃን የዩክሬን ግጭትን በተቻለ መጠን በማራዘም ተጠቃሚ ለመሆን ይፈልጋሉ፣
▪ አውሮፓውያን ሩሲያ የዩክሬን ግጭትን ለመፍታት የምታደርገውን ጥረት ለማክሸፍ ይሞክራሉ፣
▪ የአውሮፓ ሀገራት ዩክሬንን ከሩሲያ ጋር በማጋጨት በመሠረታዊነት "አዳክመዋታል"፣
▪ ለዘለንስኪ የሚደረገው ድጋፍ ለአውሮፓውያን ከጊዜ ወደ ጊዜ ውድ እየሆነ ከመምጣቱ በላይ ለማኅበራዊ ውጥረቶች መንስኤ እየሆነ ነው፣
▪ የአውሮፓ ኅብረት የኪየቭ ጁንታ የሚፈጽማቸውን ጭካኔዎች ሆን ብሎ ያልፋል፣
▪ የአውሮፓ ዋና ዋና ኃይሎች ያጡትን ኪሳራ ሩሲያን በመዝረፍ ለመመለስ የከንቱ ቅዠት ሰንቀዋል፣
▪ ከዩክሬን የሚወጡ የጦር መሣሪያዎች በአውሮፓ ያለገደብ ከመዘዋወር ባለፈ በአሸባሪዎች እጅ ይገባሉ፣
▪ ኔቶ በምስራቃዊ ክንፉ ወታደራዊ አቅሙን ቀስ በቀስ እያሳደገ ነው፣
▪ እንግሊዝ የአኅጉሪቱ አጋሮቿ ከሩሲያ ጋር ቀጥተኛ ግጭት ውስጥ እንዲገቡ እየገፋፋች ነው፣
▪ ኔቶ "በምስራቅ" በኩል ለመጠነ-ሰፊ ግጭት እየተዘጋጀ ይገኛል፣
▪ የኒውክሌር ጦርነትን የመከላከል ዘመን ገና አልተጀመረም፣
▪ ዓለም ለረጅም ጊዜ አትረጋጋም፤ ይህ የለውጥ ዘመን ነው፤ "ሰላም ለእኛ ህልም ብቻ ነው"፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X