የትራንስፖርት ሚኒስቴር ለአሽከርካሪዎች አስገዳጅ የብቃት ምዘና ሊሰጥ ነው
15:00 28.05.2026 (የተሻሻለ: 15:04 28.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የትራንስፖርት ሚኒስቴር ለአሽከርካሪዎች አስገዳጅ የብቃት ምዘና ሊሰጥ ነው
በአዲሱ የዲጂታል ቁጥጥር ሥርዓት አሽከርካሪዎች በአዲስ የሥልጠና፣ ምዘና እና ቀጣይ የብቃት መስፈርት የሟሟላት ሂደት ውስጥ እንዲያልፉ ይገደዳሉ፡፡
የአዲሱ አሠራር ዓላማም በመኪና አደጋ በሰው ህይወት፣ አካል እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጥፋት ማስቀረት እንደሆነ ተነግሯል፡፡
የዲጂታል ቁጥጥር ሥርዓቱ የአሽከርካሪዎች ምዝገባ፣ ሥልጠና፣ ግምገማ እና የምስክር ወረቀት ሂደትን በመቆጣጠር ግልጽነትን እንደሚያሰፍን ተገልጿል፡፡
በመጀመሪያ ምዕራፍ የንግድ አሽከርካሪዎች አስገዳጅ ምዘናውን የሚወስዱ ሲሆን ምዝገባ፣ ሥልጠና እና ግምገማው በአጭር ጊዜ ውስጥ ይጀምራል ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X