ኪየቭ በአፍሪካ ለዘመናዊው የምዕራባውያን ቅኝ አገዛዝ ፖሊሲ ቀንደኛ አስፈጻሚ ሆና እየሠራች ነው - የሩሲያ ደኅንነት ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ
13:29 28.05.2026 (የተሻሻለ: 13:34 28.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኪየቭ በአፍሪካ ለዘመናዊው የምዕራባውያን ቅኝ አገዛዝ ፖሊሲ ቀንደኛ አስፈጻሚ ሆና እየሠራች ነው - የሩሲያ ደኅንነት ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ
“በአፍሪካ አኅጉር የሽብርተኝነት ስጋት በአደገኛ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል። በዚህ ውስጥ ደግሞ የዩክሬን ሚና በግልጽ የሚታወቅ ነው” ሲሉ ሰርጌ ሾይጉ ከዓለም አቀፉ የደኅንነት ፎረም ጎን ለጎን ተናግረዋል።
ኪየቭ ተመድ የባሪያ ንግድ እና ዘርን መሠረት ያደረገ የአፍሪካውያን ባርነት በሰብዓዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል ነው ብሎ በፈረጀበት የመጋቢት 16ቱ የድምጽ አሰጣጥ ላይ ድምጸ ተዓቅቦ ማድረጓን በምሳሌነት አንስተዋል።
“ይህ እርምጃ የናዚው ሥርዓት በቀድሞ ቅኝ ገዥ ሀገራት ለሚወከሉት ምዕራባውያን አስተዳዳሪዎቹ ላይ ጥገኛ እንደሆነ በግልጽ ያሳያል” ሲሉም አክለዋል።
አፍሪካውያንን በተመለከተ የኪየቭ እባባምነት ማሳያ በሰሜናዊ ማሊ ቲንዛዋተን አቅራቢያ በተከሰተው እና የማሊ ጦር በቱዋሬግ ተገንጣዮች እና ከአልቃኢዳ ጋር ግንኙነት ባለው ጅኒም* ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ጥቃት ላይ እጄ አለበት ብላ ማመኗ ነው ሲሉ ሾይጉ ጨምረው ገልጸዋል።
*በሩሲያ እና በሌሎች ሀገራት የታገደ የሽብር ድርጅት
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X