- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምግብ ዋስትና በኢትዮጵያ፦ ከፖሊሲ ወደ ተግባር

የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምግብ ዋስትና በኢትዮጵያ፦ ከፖሊሲ ወደ ተግባር
ሰብስክራይብ

"የምግብ ስርዓት የምንለው ከምርት ጀምሮ እያንዳንዱ ሂደት አልፎ ምግብ የሸማቹ አፍ ውስጥ እስከሚገባ ድረስ ያለውን አጠቃላይ ሰንሰለት ነው።... የአየር ንብረት ለውጥ በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ የዕሴት ሰንሰለቱ ላይ ምርታማነትንና ፍጆታን አደጋ ላይ የሚጥሉ መዛባቶችን እየፈጠረ ነው። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምግብ ሥርዓት መገንባት ማለት ሥርዓቱ እነዚህን አስደንጋጭ ክስተቶች መቋቋም እንዲችል ማድረግ ነው፤ በዚህም የቤተሰብን ኑሮ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በዘላቂነት ማስቀጠል ይቻላል።" ሲሉ በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ሰላማዊት ገብረእግዚአብሔር (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

የአየር ንብረት መዛባት እና የአፈር መጎሳቆል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን አነስተኛ አራሾችን ህልውና እየፈተኑ ይገኛሉ። ግብርናን ከምርት መጨመር ባለፈ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም፣ ዘላቂነት እና ሉአላዊነትን ባገናዘበ መልኩ እንዴት መቅረፅ እንችላለን? የፖሊሲ ማዕቀፎችስ በምድር ላይ ያለውን እውነታ በትክክል እያስተናገዱ ነው?
በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅትበፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ሰላማዊት ገብረእግዚአብሔር (ዶ/ር) ጋር ያደረግነውን ጥልቅ ቆይታ ይዘንላችሁ ቀርበናል።

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን መረጃ ያድምጡ ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0