የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወደ ቻይና ለሚላኩ ምርቶች የወጪ ንግድ ፈቃድ በሁሉም ባንኮች እንዲሰጥ ፈቀደ
10:58 26.05.2026 (የተሻሻለ: 11:04 26.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወደ ቻይና ለሚላኩ ምርቶች የወጪ ንግድ ፈቃድ በሁሉም ባንኮች እንዲሰጥ ፈቀደ
ባንኩ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ እንዳመላከተው፣ ቀደም ሲል ወደ ቻይና ለሚላኩ ምርቶች የወጪ ንግድ ፈቃድ የሚሰጠው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል ብቻ እንዲሆን ተጥሎ የነበረው ገደብ ሙሉ በሙሉ ተነስቷል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው የሀገሪቱን የወጪ ንግድ ዘርፍ ይበልጥ ለማቅለል፣ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ እና ለላኪዎች ምቹና ተደራሽ የባንክ አገልግሎት ለመፍጠር ታስቦ መሆኑ ገልጿል።
በዚህም መሠረት ከዛሬ ጀምሮ ፈቃድ ያላቸው ሁሉም የንግድ ባንኮች ከተለመዱት የወጪ ንግድ እና የውጭ ምንዛሬ መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ ለደንበኞቻቸው አገልግሎቱን መስጠት እንዲጀምሩ ብሔራዊ ባንክ አሳስቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X