- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ከአፍሪካ ሉዓላዊነት እስከ ባለብዙ-ዋልታ ዓለም

ከአፍሪካ ሉዓላዊነት እስከ ባለብዙ-ዋልታ ዓለም
ሰብስክራይብ
"ይህ (በሀገር ውስጥ ምንዛሬ የመገበያየት ሞዴል) አገሮችን በፋይናንስ ማዕቀብ ከሚያስረው ስዊፍት [Swift] የክፍያ ስርዓት ለመውጣት ጥሩና ውጤታማ መንገድ ነው ብዬ አምናለሁ። ይህ ሞዴል የደቡባዊው ንፍቀ ክበብ ሀብት በምዕራባውያን ኃይሎች እጅ እንዲያዝ እና እንዲወረስ ተጋላጭ ከማድረግ ይልቅ፣ እዚሁ በደቡባዊው ንፍቀ ክበብ ውስጥ ተከማችቶ ለሕዝብ ጥቅም እንዲውል መንገድ ይከፍታል።" ሲሉ በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ጀማል መሀመድ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ጀማል መሀመድ (ዶ/ር) ጋር በመሆን እ.ኤ.አ በግንቦት 19 እና 20 ፣ 2026 ወር አጋማሽ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በቻይና ያደረጉትን ይፋዊ ጉብኝት ተከትሎ ሞስኮ እና ቤጂንግ የፈረሙት ታሪካዊው የጋራ መግለጫ ለአዲሱ የዓለም የኃይል ሚዛን ምን ትርጉም አለው? የሚለውን የምንቃኝ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ፣ በየዓመቱ ግንቦት 17 የሚከበረውን የአፍሪካ ቀን ለአህጉሪቱ እውነተኛ ነፃነት እና ሉዓላዊነት ምን አዲስ ጥያቄዎችን እና የቤት ስራዎችን ይዞልን መጥቷል? የሚለውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካና እስያ ጥናት ማዕከል መምህር ጌታቸው ካሳ(ዶ/ር) እና የታሪክ እና ቅርስ ጥበቃ ስርአተ-ትምህርት ባለሙያ ከሆኑት ከአቶ ተረፈ ወርቁ ጋር ተወያይተንበታል፡፡

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0