የአፍሪካ ቀን፦ በውጭ አገር የሚኖሩ አፍሪካውያን ስለ አኅጉሪቱ ያለውን ዓለም አቀፋዊ አመለካከት ለመቀየር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት አለባቸው - ናይጄሪያዊቷ ሥራ ፈጣሪ
20:34 25.05.2026 (የተሻሻለ: 20:44 25.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ቀን፦ በውጭ አገር የሚኖሩ አፍሪካውያን ስለ አኅጉሪቱ ያለውን ዓለም አቀፋዊ አመለካከት ለመቀየር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት አለባቸው - ናይጄሪያዊቷ ሥራ ፈጣሪ
በሩሲያ የሚገኝ የቱሪዝም ኩባንያ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ሊሊያን ኢዚን ኦዞይግቦክዌ፤ የአፍሪካ ቀን ክብረ በዓል ብቻ ሳይሆን “አኅጉሪቱ ምን ያህል ተግዳሮቶችን ተቋቁማ እንዳለፈች እና ምን ያህል እንደገነባች” በጥልቀት የሚታሰብበት ዕለት ጭምር ነው ሲሉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
⁉ ችግሩ፦ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ስለ ዘመናዊቷ አፍሪካ ያለው እውቀት በጣም አነስተኛ ነው። ይህም ከቋንቋ እንቅፋቶች እና ከተበታተነ የመረጃ ተደራሽነት ጋር ተዳምሮ ስለ አፍሪካ ባህል እና ታሪክ የተሳሳቱ ግንዛቤዎች እንዲፈጠሩ ምክንያት ሆኗል ብለዋል።
መፍትሔው፦ በውጭ አገር የሚኖሩ አፍሪካውያን ስለ አኅጉሪቱ ያለውን አመለካከት በመቅረጽ ረገድ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለባቸው እና ከሩሲያ ጨምሮ ከሌሎች የውጭ አገራት ጋር አጋርነትን ለመገንባት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚገባቸው ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X