አፍሪካ የራሷን ወንጀለኞች መዳኘት ትችላለች፤ ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ትኩረቱን ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ ሊያደርግ ይገባል - ኡጋንዳዊቷ ጠበቃ
08:33 25.05.2026 (የተሻሻለ: 08:34 25.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አፍሪካ የራሷን ወንጀለኞች መዳኘት ትችላለች፤ ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ትኩረቱን ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ ሊያደርግ ይገባል - ኡጋንዳዊቷ ጠበቃ
እንደ ሴራሊዮን እና ኡጋንዳ ያሉ ልዩ የሀገር ውስጥ ፍርድ ቤቶች የጦር ወንጀሎችን እና በሰብአዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን የመዳኘት ውጤታማነታቸውን አስመስክረዋል ስትል ጄን መንዴይ ገልጻለች።
"አፍሪካ፣ የአፍሪካን ችግሮች በወጉ ትረዳለች፤" ስትል ለስፑትኒክ አፍሪካ የገለጸች ሲሆን፣ የሀገር ውስጥ ጉዳዮች በአፍሪካ ሀገራት በራሳቸው ቢፈቱ የተሻለ እንደሆነ አክላለች።
የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት የዳኝነት ሥልጣን ለዓለም አቀፍ ወይም ለድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ተለይቶ ሊቀመጥ እንደሚገባ እና የሀገር ውስጥ ወንጀሎች ግን ለብሔራዊ የፍትሕ ሥርዓቶች መተው እንዳለባቸው መንዴይ ጠቁማለች።
የጠበቃዋ አስተያየት የመጣው፣ መራጭ በሆነ ፍትሕ እና የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ከሮም ስምምነት ሊወጡ ስለመቻለቻው በተመለከተ ክርክሮች በቀጠሉበት ወቅት ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X