የአፍሪካ ቀን፦ ፈጠራ ብዝኃነትን ወደ አኅጉራዊ ጥንካሬ እንዴት እንደሚቀይር ናይጄሪያዊው ሥራ ፈጣሪ ያብራራል
08:01 25.05.2026 (የተሻሻለ: 08:04 25.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ቀን፦ ፈጠራ ብዝኃነትን ወደ አኅጉራዊ ጥንካሬ እንዴት እንደሚቀይር ናይጄሪያዊው ሥራ ፈጣሪ ያብራራል
የአፍሪካ የፈጠራ ጥበብ ወግን እና ዘመናዊነትን አጣምሮ የያዘ በመሆኑ ከፍተኛ ኃይል አለው፤ ሲል ለስፑትኒክ አፍሪካ የገለጸው ናይጄሪያው ሥራ ፈጣሪ ኪንግስሊ ቹክዉሜካ ኦዞይግቦክዌ ለእሱ የአፍሪካ ቀን የተለያዩ ቋንቋዎች፣ ባህሎች እና አመለካከቶች የመከፋፈያ መንገዶች ሳይሆኑ የጥንካሬ ምንጮች የሆኑበት አንድነትን የሚያከብርበት ነው።
"ከበርካታ ዓመታት በፊት፣ ከሌሎች አኅጉራት የመጡ ሰዎች [...] አፍሪካን እንደ 'ጫካ' ይመለከቷት ነበር። ስለዚህ የፈጠራ ኢንዱስትሪው አፍሪካ ከዚያ በላይ የሆነችና ለዓለም የምታሳየው ብዙ ነገር እንዳላት ለማሳየት መጥቷል" በማለት ተናግሯል።
በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት ውስጥ የፈጠራ ኢንዱስትሪዎች በመላው አኅጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የቱሪዝም፣ የቴክኖሎጂ እና የኢኮኖሚ ዕድገት አንቀሳቃሽ ኃይል እንደሚሆኑ ያምናል።
የአፍሪካ ቀን የተሰጥኦ ማሳያ አከባበር ብቻ ሳይሆን ወጣት አፍሪካውያን እንዲተባበሩ፣ አዳዲስ ነገሮችን እንዲፈጥሩ እና የአኅጉሪቱን አቅም ወደ እውነተኛ ለውጥ እንዲቀይሩ የቀረበ የድርጊት ጥሪ መሆኑን አጽንኦት ሰጥቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X