ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ በልዩ ሕክምና ዘርፍ ከሚሰለጥኑ የሩዋንዳ ባለሙያዎች ጋር ማዕድ ቆረሱ

© telegram sputnik_ethiopiaጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ በልዩ ሕክምና ዘርፍ ከሚሰለጥኑ የሩዋንዳ ባለሙያዎች ጋር ማዕድ ቆረሱ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ በልዩ ሕክምና ዘርፍ ከሚሰለጥኑ የሩዋንዳ ባለሙያዎች ጋር ማዕድ ቆረሱ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 24.05.2026
ሰብስክራይብ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ በልዩ ሕክምና ዘርፍ ከሚሰለጥኑ የሩዋንዳ ባለሙያዎች ጋር ማዕድ ቆረሱ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በኢትዮጵያ በልዩ የሕክምና ዘርፍ ሥልጠና ላይ ከሚገኙ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ባለሙያዎች መካከል፣ ከሩዋንዳ ለመጡ 128 የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በጋራ ማዕድ መቁረሳቸውን አስታውቀዋል።

"እነዚህ ባለሙያዎች የአኅጉራችን የጤና ዘርፍ የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚጠይቀውን ከፍተኛ ዕውቀትና የላቀ ብቃት ለማሟላት ታምነው እየተጉ ያሉ ናቸው" ብለዋል።

ባለሙያዎቹ የሚሰለጥኑባቸው ተቋማትም ቀጣዩን አፍሪካዊ ትውልድ በሕክምናው ዘርፍ የሚኖረውን የመሪነት ሚና በማረጋገጥ ላይ የሚገኙ መሆናቸውን የኢትዮጵያው መሪ ጠቁመዋል።

"በጋራ ዕውቀትና ዓላማ፣ ይበልጥ ጤናማ የሆነች አፍሪካን አብረን መገንባታችንን እንቀጥላለን" ሲሉ በማኅበራዊ ሚዲያቸው ላይ ጽፈዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ በልዩ ሕክምና ዘርፍ ከሚሰለጥኑ የሩዋንዳ ባለሙያዎች ጋር ማዕድ ቆረሱ - Sputnik አፍሪካ
1/2
© telegram sputnik_ethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ በልዩ ሕክምና ዘርፍ ከሚሰለጥኑ የሩዋንዳ ባለሙያዎች ጋር ማዕድ ቆረሱ - Sputnik አፍሪካ
2/2
1/2
2/2
አዳዲስ ዜናዎች
0