ዚምባብዌ የአማራጭ ገበያዎችን በር ለመክፈትና ከምዕራባውያን የፋይናንስ የበላይነት ለማምለጥ በብሪክስ ባንክ ላይ ተስፋ ጥላለች - መገናኛ ብዙኃን

© telegram sputnik_ethiopiaዚምባብዌ የአማራጭ ገበያዎችን በር ለመክፈትና ከምዕራባውያን የፋይናንስ የበላይነት ለማምለጥ በብሪክስ ባንክ ላይ ተስፋ ጥላለች - መገናኛ ብዙኃን
ዚምባብዌ የአማራጭ ገበያዎችን በር ለመክፈትና ከምዕራባውያን የፋይናንስ የበላይነት ለማምለጥ በብሪክስ ባንክ ላይ ተስፋ ጥላለች - መገናኛ ብዙኃን - Sputnik አፍሪካ, 1920, 24.05.2026
ሰብስክራይብ

ዚምባብዌ የአማራጭ ገበያዎችን በር ለመክፈትና ከምዕራባውያን የፋይናንስ የበላይነት ለማምለጥ በብሪክስ ባንክ ላይ ተስፋ ጥላለች - መገናኛ ብዙኃን

አገሪቱ የ3.3 ቢሊዮን ሕዝብ እና ከ45 ትሪሊዮን ዶላር በላይ የሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ያለውን አማራጭ ገበያ ለመጠቀም፣ ወደ ስብስቡ እና ወደ አዲሱ የልማት ባንክ ለመቀላቀል እየገፋችበት መሆኑን ዘ ሄራልድ ዘግቧል።

ይህ እርምጃ አገሪቱን ምዕራባውያን ከሚመሩት የፋይናንስ ሥርዓቶች ሊጠብቃት የሚችል ስትራቴጂካዊ “ጨዋታ ለዋጭ” ተደርጎ እንደሚታይም ተገልጿል።

ሙሉ አባልነት ማግኘት፣ ሐራሬ ለሕዝብ መሠረተ-ልማት እና ዘላቂ ልማት የሚሆን የባንኩን 100 ቢሊዮን ዶላር ካፒታል ያለ ምንም የፖለቲካ ቅድመ-ሁኔታ እንድትጠቀም የሚያስችላት ሲሆን፣ ይህም በምዕራባውያን ዕርዳታ ላይ ያለባትን ከልክ ያለፈ ጥገኝነት እንደሚቀንስላት በዘገባው ላይ ተመልክቷል።

ዚምባብዌ በአሁኑ ጊዜ ባንኩን ለመቀላቀል የመጨረሻ ድርድሮችን እያደረገች ሲሆን፣ ስምምነቱም በፓርላማ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ዕትሙ ጠቁሟል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0