የቻይና አቶሚክ ኃይል ባለሥልጣን የኢትዮጵያን የኒውክሌር ፕሮግራም ለማገዝ ፍላጎት እንዳለው ገለጸ
16:00 23.05.2026 (የተሻሻለ: 16:04 23.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የቻይና አቶሚክ ኃይል ባለሥልጣን የኢትዮጵያን የኒውክሌር ፕሮግራም ለማገዝ ፍላጎት እንዳለው ገለጸ
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳንዶካን ደበበ፤ በቻይና የአቶሚክ ኢነርጂ ባሥስልጣን ምክትል ሊቀመንበር ሊ ጂንግ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በቢሯቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው።
ሁለቱ ወገኖች በኒውክሊየር ዘርፍ ስትራቴጂካዊ ትብብር፣ በሰው ኃይል ልማት እና በተቋማዊ አቅም ግንባታ ዙሪያ ፍሬያማ የሁለትዮሽ ምክክር አድርገዋል።
ዘላቂ የኒውክሊየር ኃይል ማዕቀፎችን ለመዘርጋት በሚረዱ የፋይናንስ ስትራቴጂዎችና የቁጥጥር ደረጃዎች ላይ ዝርዝር ምክክር እንደተካሄደም የኢትዮጵያ ኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X