ግብፅ ቀጣናዊ የእህል ማዕከል ለመሆን ከሩሲያ ጋር ግንኙነቷን ይበልጥ ማጥበቅ ትፈልጋለች - የሀገሪቱ ሚኒስትር
ግብፅ ቀጣናዊ የእህል ማዕከል ለመሆን ከሩሲያ ጋር ግንኙነቷን ይበልጥ ማጥበቅ ትፈልጋለች - የሀገሪቱ ሚኒስትር
ግብፅ የቀጣናው የእህል ማከማቻ፣ ማቀነባበሪያ እና የንግድ ማዕከል ለመሆን የሚያስችላትን ስትራቴጂ በመከተል ላይ መሆኗን የሀገሪቱ የአቅርቦት ሚኒስትር ሸሪፍ ፋሩክ በሩሲያ ሶቺ በተካሄደው የእህል ፎረም ላይ አስታውቀዋል።
ይህ ተነሳሽነት የግብፅን ስልታዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ በጥሩ ሁኔታ የሚጠቀም እና የምርት ብክነትን ለመቀነስ በዘመናዊ የእህል ጎተራዎች፣ በትራንስፖርት ሥርዓቶች እና በዲጂታል የክትትል ዘዴዎች ላይ የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶችን ያጠቃልላል ብለዋል።
ፋሩክ ግብፅ አሁንም ከሩሲያ ከፍተኛ ስንዴ ከሚያስገቡ ሀገራት እንደሆነች እና ይህን ትብብር ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ሩሲያ እ.ኤ.አ በ2025 8.5 ሚሊዮን ቶን ስንዴ ለግብፅ ማቅረቧን እና በ2026 ደግሞ እስካሁን 4.58 ሚሊዮን ቶን መላኩን ጠቅሰው፤ በከፍተኛ ቴክኖሎጂ መሠረተ-ልማት እና በምርት ልውውጥ ዘርፎች በጋራ ፕሮጀክቶች ለመሰማራት የሚያስችሉ ዕድሎችን አንስተዋል።
የግብፅ ግብ የምግብ ዋስትናን የሚያጠናክር እና ሀገሪቱን በዓለም አቀፍ የእህል ንግድ ውስጥ ቁልፍ አስተሳሳሪ የሚያደርግ የተቀናጀ ሥርዓት መገንባት እንደሆነ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X