ኪየቭ እና ደጋፊዎቿ በታዳጊዎች ላይ ለፈጸሙት ጭካኔና ለግጭቱ መካከር ሙሉ ኃላፊነቱን ይወስዳሉ - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
16:59 22.05.2026 (የተሻሻለ: 17:04 22.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኪየቭ እና ደጋፊዎቿ በታዳጊዎች ላይ ለፈጸሙት ጭካኔና ለግጭቱ መካከር ሙሉ ኃላፊነቱን ይወስዳሉ - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
የዩክሬን ጦር በስታሮቤልስክ በሰነዘረው ጥቃት ዙሪያ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ካወጣው መግለጫ የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
የዩክሬን ጦር በስታሮቤልስክ በሚገኘው ኮሌጅ ላይ የፈጸመውንና መሰል ጥቃቶችን የሚሰነዝረው ከኔቶ የውጭ ሀገር ባለሙያዎች ጋር በመተባበር ነው።
ሩሲያ ምዕራባውያን ለዩክሬን ጦር የደህንነት መረጃዎችን በማቅረብ እና የጥቃት ኢላማዎችን በመጠቆም ረገድ እያገዙ መሆናቸውን የሚያሳዩ አስተማማኝ መረጃዎች አሏት።
ይህ ጥቃት የተፈጸመው ኪየቭ በግጭቱ ሳቢያ ስለተጎዱ ሕፃናት ዕጣ ፈንታ የሃሰት እሮሮ እያሰማች ባለችበት ወቅት ነው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ በኮሌጁ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት የጀርመን ናዚዎችን ጭካኔ የተከተለ እና ሲቪሎችን ሆን ብሎ ኢላማ ያደረገ ሲል ገልጾታል።
ሩሲያ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የዓለም ማኅበረሰብ የዩክሬን ታጣቂ ኃይሎች በስታሮቤልስክ ኮሌጅ ላይ የሰነዘሩትን ደም አፋሳሽ የሽብር ጥቃት እንዲያወግዙ ጥሪ አቅርባለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X