ማሊ በሩሲያ ጦር የአፍሪካ ኮር ድጋፍ መጠነ-ሰፊ የጽንፈኛ ሙስሊም ጥቃቶችን መከተች - የሩሲያ የደኅንነት ምክር ቤት

ሰብስክራይብ

ማሊ በሩሲያ ጦር የአፍሪካ ኮር ድጋፍ መጠነ-ሰፊ የጽንፈኛ ሙስሊም ጥቃቶችን መከተች - የሩሲያ የደኅንነት ምክር ቤት

​ የሩሲያ የደኅንነት ምክር ቤት ምክትል ፀሐፊ አሌክሳንደር ቬኔዲክቶቭ ለስፑትኒክ እንደተናገሩት፤ የአፍሪካ ኮር ክፍሎች የማሊ ኃይሎች የጂሃዲስት ጥቃቶችን እንዲመክቱ እና በባማኮ እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ቁልፍ ይዞታዎችን ነፃ እንዲያወጡ አግዘዋል።

የጋራ ኦፕሬሽኑ ሩሲያ ከአፍሪካ አጋሮቿ ጋር የምታደርገው ትብብር ውጤታማ መሆኑን አረጋግጧል ብለዋል።

​ ሩሲያ በውጊያ ዝግጁነት፣ በወታደራዊ ሥልጠና፣ በሕግ ማስከበር እና በደኅንነት ላይ በማተኮር በባለብዙ ወገን እና በሁለትዮሽ መድረኮች ለአፍሪካ ሀገራት ድጋፍ እንደምታደርግም ገልጸዋል።

​ሞስኮ ከግንቦት 18 እስከ 21 የሩሲያ የደኅንነት ምክር ቤት በሚያስተናግደው የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የደኅንነት መድረክ ላይ የ50 አፍሪካ ሀገራት ልዑካን ቡድን እንደሚጠበቅ አስታውቃለች። በዚህ መድረክ ከ180 በላይ ሀገራትና ድርጅቶች ተጋብዘዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0