የዚምባብዌ የማዕድን ዘርፍ እስከ 2030 ድረስ 100 ሺህ የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራል - የሀገሪቱ የማዕድን ምክር ቤት
18:46 21.05.2026 (የተሻሻለ: 18:54 21.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዚምባብዌ የማዕድን ዘርፍ እስከ 2030 ድረስ 100 ሺህ የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራል - የሀገሪቱ የማዕድን ምክር ቤት
በሀገሪቱ ሕጋዊ የማዕድን ዘርፍ ከሚፈጠሩት አዳዲስ የሥራ ዕድሎች መካከል ወደ ግማሽ የሚጠጋውን ድርሻ የሚይዙት መሐንዲሶችና የቴክኒክ ባለሙያዎች ናቸው ሲል ምክር ቤቱ አስታውቋል።
የምክር ቤቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አይዛክ ክዌሱ፤ "ሕጋዊው የማዕድን ኢንዱስትሪ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ በትንሹ 100 ሺህ የሰው ኃይል ይፈልጋል፤ ከእነዚህም ውስጥ ግማሽ ያህሉ ከፍተኛ ሙያዊ ክህሎት ያላቸው ባለሙያዎች፣ በተለይም መሐንዲሶች ናቸው" ብለዋል።
በወርቅ፣ በሊቲየም፣ በፕላቲነም እና በክሮም ማዕድናት ላይ የሚደረጉ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች ለዘርፉ ፈጣን መስፋፋት ዋነኛ መንስኤ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ወቅት ሕጋዊው የማዕድን ዘርፉ 60 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደፈጠረ፣ ለሀገሪቱ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት 14.5 በመቶ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ፣ የ7.7 ቢሊዮን ዶላር ምርት እንደሚወጣበት እና ከ8 ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ እንደሚፈስበት የምክር ቤቱ መረጃ ይጠቁማል።
የማዕድን ዘርፉ እ.ኤ.አ በ2025 የ7.3 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን ዘንድሮ ደግሞ የ10 በመቶ ዕድገት ያሳያል ተብሎ ይጠበቃል። ይህም ከፍተኛ የሰው ኃይል ፍላጎት እንደሚፈጥር ክዌሱ ተናግረዋል።
⌨ በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X