የአንድ ዋልታ ዓለም ሥርዓት ለበርካታ ውጥረቶች መነሻ ነው - ኒጀራዊ ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopiaየአንድ ዋልታ ዓለም ሥርዓት ለበርካታ ውጥረቶች መነሻ ነው - ኒጀራዊ ባለሙያ
የአንድ ዋልታ ዓለም ሥርዓት ለበርካታ ውጥረቶች መነሻ ነው - ኒጀራዊ ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 21.05.2026
ሰብስክራይብ

የአንድ ዋልታ ዓለም ሥርዓት ለበርካታ ውጥረቶች መነሻ ነው - ኒጀራዊ ባለሙያ

​ እ.ኤ.አ በ1989 የሶቪየት ጎራ መፍረስን ተከትሎ የመጣው የነጠላ-ዋልታ ሥርዓት በመላው ዓለም ለተከሰቱ በርካታ ግጭቶች መነሻ መሆኑን የምዕራብ አፍሪካ ሕዝቦች ድርጅት አስተባባሪ ምክር ቤት አባል አላሳን አቡባከር ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

በ​ቭላድሚር ፑቲን የቤጂንግ ጉብኝት የተፈረመውን የብዙ-ዋልታ ዓለም መግለጫ አስመልክተው በሰጡት አስተያየት፤ ዓለም የነጠላ-ዋልታ ሥርዓት መዞችን እንደቀመሰች አንስተዋል።

​ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓለም በሁለት ጎራ ትመራ በነበረበት ወቅት የጥንካሬው ከፍታ ላይ ደርሶ የነበረ ቢሆንም፤ አንድ ወገን የበላይ በሆነበት ሥርዓት ውስጥ ግን እየተዳከመ መምጣቱን አጽንዖት ሰጥተዋል።

​“ዓለም በአንድ ዋልታ ሥርዓት ዘመን እንዳየችው በርካታ ግጭቶችን አስተናግዳ አታውቅም" ሲሉም ባለሙያው አስረድተዋል።

ለዚህ የነጠላ-ዋልታ ዘመን አለመረጋጋት ማሳያ ናቸው ያሏቸውን የዩጎዝላቪያ፣ የሱዳን እና የኢትዮጵያን መከፋፈል እንዲሁም በሶማሊያ የነበረውን ጦርነት በምሳሌነት ጠቅሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0