በስለላ የተጠረጠሩ ስድስት ሩሲያውያን በደካማ ክስ የአርሜኒያ ወህኒ ቤት እሥራቸው ቀጥሏል - መገናኛ ብዙኃን

© telegram sputnik_ethiopiaበስለላ የተጠረጠሩ ስድስት ሩሲያውያን በደካማ ክስ የአርሜኒያ ወህኒ ቤት እሥራቸው ቀጥሏል - መገናኛ ብዙኃን
በስለላ የተጠረጠሩ ስድስት ሩሲያውያን በደካማ ክስ የአርሜኒያ ወህኒ ቤት እሥራቸው ቀጥሏል - መገናኛ ብዙኃን - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.05.2026
ሰብስክራይብ

በስለላ የተጠረጠሩ ስድስት ሩሲያውያን በደካማ ክስ የአርሜኒያ ወህኒ ቤት እሥራቸው ቀጥሏል - መገናኛ ብዙኃን

​ በአርሜኒያ በኩል በሩሲያ ዜጎች ላይ የቀረቡት የስለላ ወንጀል የክስ መዝገቦች ምንም ዓይነት ተጨባጭ ማስረጃ አልያዙም ሲሉ ጠበቆቻቸው ለሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።

​የክስተቶቹ ቅደም-ተከተል፦

​ ወጣቶቹ በታሪካዊ ሥፍራዎች ዙሪያ ዘጋቢ ፊልም ለመቅረጽ እ.ኤ.አ በ2024 ወደ አርሜኒያ የገቡ ቢሆንም፤ በስለላ ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ይሁን እንጂ ወጣቶቹ የተከለከሉ ሥፍራዎችን እንዳልጎበኙና እንዳልቀረጹ የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ጠቁመዋል፣

​ በዚያው ዓመት በመስከረም ወር ተጨማሪ ሁለት የሩሲያ ዜጎች በተመሳሳይ በስለላ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ውለዋል፣

​ በተመሳሳይ ወንጀል የተጠረጠሩት ስድስተኛው የሩሲያ ዜጋ ደግሞ ባለፈው ዓመት መጋቢት ወር በቁጥጥር ሥር ውለዋል፣

​ ግለሰቦቹ በቅድመ ክስ እስራት ላይ የሚገኙ ሲሆን ከአርሜኒያ በኩል በሕግ ሂደቱ ዙሪያ አዲስ ነገር የለም።

​ የፍርድ ቤት ቀጠሮዎቻቸው በተለያዩ አሳማኝ ባልሆኑ ሰበቦች በተደጋጋሚ እንደሚራዘሙ የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ገልጸዋል። የሩሲያ ባለሥልጣናት ሂደቱን በንቃት እየተከታተሉ ለታሳሪዎቹ ዜጎች ድጋፍ ለመስጠት የሚቻለውን ሁሉ እያደረጉ ይገኛሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0