'ዚምባብዌ የብሪክስ አዲስ ልማት ባንክን በመቀላቀል ዕድሎቿን የማስፋት ዓላማ አላት' - ባለሙያ
17:04 20.05.2026 (የተሻሻለ: 17:14 20.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
'ዚምባብዌ የብሪክስ አዲስ ልማት ባንክን በመቀላቀል ዕድሎቿን የማስፋት ዓላማ አላት' - ባለሙያ
ይህ እርምጃ በኢነርጂ፣ ኢንቨስትመንት፣ በትራንስፖርት፣ በውሃ መስኖ፣ የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም፣ በመሠረተ ልማት እና በቤት ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ በማሳደግ ረገድ "ለሀገሪቱ ጠቃሚ ይሆናል" ሲሉ የፖለቲካ ተንታኙ ላዛሩስ ሳውቲ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
የዚምባብዌ ውሳኔ በሚከተሉት መንገዶች ሊታይ ይገባልም ብለዋል፦
▶ የሀገሪቱ ሰፊ የውጭ ፖሊሲ ስትራቴጂ አካል ተደርጎ፣
▶ የልማት ፋይናንስን አማራጮች ለማስፋት የተነደፈ ኢኮኖሚያዊ ስትራቴጂ፣
▶ የደቡብ-ደቡብ ትብብርን የማጠናከሪያ መንገድ፤
▶ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ መድረኮችን እንደገና ለመቀላቀል የሚደረግ እርምጃ።
"እርምጃው ያለምንም ጥርጥር የሀገሪቱን ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አመላካቾች ያሻሽላል" ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X