ሶማሊያ፤ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ማቀዷን አስታወቀች

© telegram sputnik_ethiopiaሶማሊያ፤ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ማቀዷን አስታወቀች
ሶማሊያ፤ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ማቀዷን አስታወቀች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.05.2026
ሰብስክራይብ

ሶማሊያ፤ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ማቀዷን አስታወቀች

የሀገሪቱ የኢነርጂ ሚኒስትር አብዱላሂ ቢድሃን ዋርሳሜ፤ “የሶማሊያ መንግሥት ከጎረቤት ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስገባት በሚቻልበት መንገድ ዙሪያ እየሠራ ነው” ሲሉ ለሚዲያ ተናግረዋል፡፡

 

መንግሥታቸው የኤሌክትሪክ ኃይሉን በሦስት መግቢያ መስመሮች ማለትም በዶሎው፣ በዋጃሌ እና በጎልዶጎብ በኩል በማስገባት በመላ ሀገሪቱ ለሚገኙ ከተሞች ለማሠራጨት ማቀዱን ገልጸዋል።

 

ለሁለቱ የታቀዱ የማስተላለፊያ መስመሮች የተደረገው የአዋጭነት ጥናት አስቀድሞ መጠናቀቁንም ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል።

 

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀንድ ሀገራት መካከል ለኬንያ፣ ጅቡቲ፣ ታንዛኒያ እና ሱዳን የኤሌትሪክ ሽያጭ እያከናወነች መሆኑ ይታወቃል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0