ኢትዮጵያ እና ቻይና የኢንቨስትመንት ትብብራቸውን ለማጠናከር ያለመ ውይይት አካሄዱ

© telegram sputnik_ethiopiaኢትዮጵያ እና ቻይና የኢንቨስትመንት ትብብራቸውን ለማጠናከር ያለመ ውይይት አካሄዱ
ኢትዮጵያ እና ቻይና የኢንቨስትመንት ትብብራቸውን ለማጠናከር ያለመ ውይይት አካሄዱ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.05.2026
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ እና ቻይና የኢንቨስትመንት ትብብራቸውን ለማጠናከር ያለመ ውይይት አካሄዱ

 

የቻይና ባለሃብቶች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዘለቀ ተመስገን በቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ የመንግሥት ምክር ቤት አማካሪ ከተመራ ልዑክ ጋር ባደረጉት ውይይት ተናግረዋል።

 

“...በተለይም በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ በግብርና፣ በማዕድን፣ በቴክኖሎጂ እና በቱሪዝም ዘርፎች ያሉ ሰፊ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ለቻይና ባለሀብቶች ክፍት ናቸው” ብለዋል።

 

የቻይና ልዑክ መሪ ዡ ሺያዶንግ በበኩላቸው፤ ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የረጅም ጊዜ ወዳጅነትና የኢኮኖሚ ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል ሲል የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0