ምሁራን በአፍሪካ ትክክለኛ ችግሮች ላይ እንዳያተኩሩ የገንዘብ እጥረት እንቅፋት ሆኖባቸዋል - ኢትዮጵያዊት ምሁር

ሰብስክራይብ
ምሁራን በአፍሪካ ትክክለኛ ችግሮች ላይ እንዳያተኩሩ የገንዘብ እጥረት እንቅፋት ሆኖባቸዋል - ኢትዮጵያዊት ምሁር


በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ዶክተር ኢትዮጵያ ለገሰ፣ "እኛ እንደ ምሁራን የምንሳተፍባቸውን የምርምር ፕሮጀክቶችን ብትመለከት፣ የገንዘብ ድጋፍ ምንጫቸው ከአኅጉሪቱ ውጭ ነው። በዚህም ድጋፍ የሚያደርጉ ድርጅቶች አጀንዳዎች ስንከተል አኅጉራዊ ጉዳዮችን ወደጎን ስንል ልንታይ እንችላለን።" ብለዋል።


ዶክተር ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የቢዝነስ ትምህርት ቤቶች ማኅበር ዓመታዊ ጉባኤ ጎን ለጎን ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት አስተያየት፣ የምሁራኑን ክፍተት መሙላት ያስቸሰላል ያሉትን መፍትሔም ጠቁመዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0