የዓለም ጤና ድርጅት በኮንጎ እና በኡጋንዳ የተቀሰቀሰውን የኢቦላ ወረርሽኝ ዓለም አቀፍ የሕብረተሰብ ጤና አስቸኳይ ስጋት ሲል አወጀ
15:40 17.05.2026 (የተሻሻለ: 17:08 17.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዓለም ጤና ድርጅት በኮንጎ እና በኡጋንዳ የተቀሰቀሰውን የኢቦላ ወረርሽኝ ዓለም አቀፍ የሕብረተሰብ ጤና አስቸኳይ ስጋት ሲል አወጀ
“በኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በኡጋንዳ በቡንዲቡግዮ ቫይረስ ምክንያት የተከሰተው የኢቦላ በሽታ ዓለም አቀፍ ስጋት የሆነ የሕብረተሰብ ጤና አስቸኳይ አዋጅ የሚደነገግበት ቢሆንም፣ የወረርሽኝ መስፈርቶችን ግን አያሟላም” ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።
ይህ አስቸኳይ አዋጅ የተቀናጀ ዓለም አቀፍ ምላሽን የሚሻ ሲሆን፣ አገራት በዓለም አቀፍ የጤና ደንቦች መሠረት እርምጃ የመውሰድ ሕጋዊ ግዴታ አለባቸው።
የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል መረጃ እንደሚያሳየው፤ እስካሁን ድረስ በኮንጎ 13 በላቦራቶሪ የተረጋገጡ ታማሚዎች እና 4 የሞት አደጋዎች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ከዚህ በተጨማሪ 246 ተጠርጣሪዎች እና ከወረርሽኙ ጋር ሊያያዙ የሚችሉ 65 የሞት አደጋዎች በምርመራ ላይ ይገኛሉ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኡጋንዳ በወረርሽኙ ምክንያት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ዓርብ ዕለት አውጃለች። የአገሪቱ ጤና ሚኒስቴር የመጀመሪያውን የክትባት ሙከራ ተከትሎ ቀደም ሲል ተከስቶ የነበረው የኢቦላ ወረርሽኝ ማክተሙን በሚያዝያ ወር ማጠናቀቂያ ላይ ማስታወቁ ይታወሳል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
“በኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በኡጋንዳ በቡንዲቡግዮ ቫይረስ ምክንያት የተከሰተው የኢቦላ በሽታ ዓለም አቀፍ ስጋት የሆነ የሕብረተሰብ ጤና አስቸኳይ አዋጅ የሚደነገግበት ቢሆንም፣ የወረርሽኝ መስፈርቶችን ግን አያሟላም” ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።
ይህ አስቸኳይ አዋጅ የተቀናጀ ዓለም አቀፍ ምላሽን የሚሻ ሲሆን፣ አገራት በዓለም አቀፍ የጤና ደንቦች መሠረት እርምጃ የመውሰድ ሕጋዊ ግዴታ አለባቸው።
የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል መረጃ እንደሚያሳየው፤ እስካሁን ድረስ በኮንጎ 13 በላቦራቶሪ የተረጋገጡ ታማሚዎች እና 4 የሞት አደጋዎች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ከዚህ በተጨማሪ 246 ተጠርጣሪዎች እና ከወረርሽኙ ጋር ሊያያዙ የሚችሉ 65 የሞት አደጋዎች በምርመራ ላይ ይገኛሉ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኡጋንዳ በወረርሽኙ ምክንያት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ዓርብ ዕለት አውጃለች። የአገሪቱ ጤና ሚኒስቴር የመጀመሪያውን የክትባት ሙከራ ተከትሎ ቀደም ሲል ተከስቶ የነበረው የኢቦላ ወረርሽኝ ማክተሙን በሚያዝያ ወር ማጠናቀቂያ ላይ ማስታወቁ ይታወሳል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X