የኤችአይቪ ፈር ቀዳጅ መርፌ አፍሪካ ለአስቸኳይ የጤና ሉዓላዊነት ያላትን ፍላጎት ያጋልጣል - ደቡብ አፍሪካዊ ሐኪም

ሰብስክራይብ

የኤችአይቪ ፈር ቀዳጅ መርፌ አፍሪካ ለአስቸኳይ የጤና ሉዓላዊነት ያላትን ፍላጎት ያጋልጣል - ደቡብ አፍሪካዊ ሐኪም

‘ሌናካፓቪር’ የተሰኘውና በዓመት ሁለት ጊዜ የሚወሰደው አዲሱ የኤችአይቪ መከላከያ መርፌ፣ በየቀኑ የሚወሰዱትን የፕሪፕ ክኒኖች ትልቁን ችግር ማለትም የተጠቃሚዎችን ሕግጋት የማክበር (ያለማቋረጥ የመውሰድ) ተግዳሮት የሚፈታ ሲሆን፣ ለአፍሪካም ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ ሊሆን እንደሚችል ሐኪም እና አክቲቪስት የሆነው ኢንኖሰንት ቻውኬ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

አፍሪካ እንዲህ ያሉ መድኃኒቶችን በራሷ ለማምረት የሚያስችላትን አቅም ማሳደግ እንዳለባት ያሳሰቡት ቻውኬ፣ “ከመጠን በላይ ጥገኝነት ለማይፈለጉ ነገሮች ያጋልጠናል፤ በተለይም እነዚህን ነገሮች ወደ ሰውነታችን የምናስገባቸው በመሆኑ ምክንያት” ሲሉ ገልፀዋል።

በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ የኤችአይቪ ችግር ያለባቸው ትልልቅ አገራት የአፍሪካ አገራት መሆናቸውን ቻውኬ አጉልተው አሳይተዋል።

“በውጭ ኃይሎች ላይ ከመጠን በላይ መታመንን ማቆም አለብን። አንዳንድ ጊዜ እነዚህ የውጭ ኃይሎች እኛ ያለንን ዓይነት ምኞትና ዓላማ አይጋሩም። እንዲያውም አንዳንድ ጊዜ ሊረዱን የመጡ መስለው የሚቀርቡን በጣም ክፉ ኃይሎች ናቸው” ሲሉ አጠቃለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0