ብሔራዊ የገጠር መሬት አስተዳደር መረጃ ሥርዓት ለአርሶ አደሮች ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር አቅርቦት አስገኘ - ግብርና ሚኒስቴር
14:31 17.05.2026 (የተሻሻለ: 14:44 17.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ብሔራዊ የገጠር መሬት አስተዳደር መረጃ ሥርዓት ለአርሶ አደሮች ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር አቅርቦት አስገኘ - ግብርና ሚኒስቴር
የግብርና ሚኒስቴር አርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ የዘረጋው ዘመናዊው የብሔራዊ ገጠር መሬት አስተዳደር መረጃ ሥርዓት፤ ለ65 ሺህ ባለይዞታዎች ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር አቅርቦት እንዲመቻች ማድረጉን አስታውቋል።
በ18 አበዳሪ የፋይናንስ ተቋማት አማካኝነት የተገኘውን ይህንን የብድር አቅርቦት ጨምሮ ሥርዓቱ እስካሁን በ10 ክልሎች፣ በ536 ወረዳዎች መተግበሩን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
32.8 ሚሊዮን ማሳዎች ወደ መረጃ ሥርዓቱ እንዲገቡ ተደርገው 10.8 ሚሊዮን ባለይዞታዎች የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ መደረጉም ተመላክቷል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X